Tenders

የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር sc/l/wrm/002/2018

 የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር SC/L/WRM/002/2018

ኢትዮ ቴሌኮም ለድርጅቱ አገልግሎት የማይሰጡ አዳዲስ እና ከአገልግሎት የተመለሱ የተለያዩ የእጅ ሞባይሎች ቀፎዎች፤ የቤት ስልኮች እና ሞደሞች፣ የፓወር እና ኔትዎርክ ስፔር ፓርቶች፣ የፊክስድ ኔትዎርክ ዕቃዎች፣ የተለያዩ ዐይነት ዴስክ ቶፕ  ኮምፒውተር ሲፒዩ እና ሞኒተሮች፣ የተለያዩ  ዓይነት ራኮች፣ የኔትዎርክ አንቴናዎች፣ ከአገልግሎት የተመለሱ ፕሪንተሮች፣ ፋክስ ማሽኖች፤ ሲግኒቸር ፓዶች፤ ስካነሮች እና የኮምፒ አክሰሰሪዎች፣ ያገለገሉ ላፕቶፖች፣ ከአገልግሎት የተመለሱ የተለያዩ የቢሮ መገልገያ ዕቃዎች፣ የተለያዩ የመኪና ስፔር ፓርቶች፣ የተለያዩ ያገለገሉ ሰርቨሮች፣ የተለያዩ የአይሲቲ ስፔር ፓርቶች፣ ከአገልግሎት የተመለሱ ስክራኘ የፖል እንጨቶች፣ ብረታብረቶችንና ራኮችን ባሉበት ቦታና ሁኔታ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከህዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ህዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ድረስ በማንኛውም ጊዜ እና ሰዓት ከኦክሽን ኢትዮጵያ ዌብ ሳይት ወይም ከኦክሽን ኢትዮጰያ መተግበሪያ በመግባት ማግኘት እና መመዝገብ የምትችሉ ሲሆን ንብረቶቹን  መመልከት እንዲሁም ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትፈልጉ ተጫራቾች  አቃቂ  በሚገኘው የድርጅቱ ዋና ግምጃ ቤት ፣ በወሎ ሰፈር በሚገኘው የኩባንያው ዕቃ ግምጃ ቤቶች እንዲሁም በምስራቅ አዲስ አበባ (ገርጂ)፣ በሰሜን አዲስ አበባ (ፈረንሳይ) እና በምዕራብ አዲስ አበባ (አስኮ) በመገኘት የታደሰ መታወቂያችሁን በመያዝ መጎብኘትና መመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

ጨረታው ሙሉ በሙሉ የሚከናወነው በኦክሽን ኢትጵያ መተግበሪያ ብቻ ሲሆን መተግበሪያውንም ከአፕ ስቶር ወይም ኘሌይ ስቶር (Auction Ethiopia) ብለው በማውረድ ወይም www.auction.et ላይ በመመዝገብ መወዳደር ይችላሉ፡፡

የኦክሽን ኢትጵያ መተግበያ አጠቃቀምን በተመለከተ በኦክሽን ኢትጵያ የጥሪ ማዕከል 9164/ 090511-5511 ወይም 0116-66-8828 ደውሎ መረዳት ይቻላል፡፡

ኩባንያው የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም

ETHIO TELECOM

Telecommunication

ETHIO TELECOM

ethiotelecom.et

Ethio telecom, previously known as the Ethiopian Telecommunications Corporation, is an Ethiopian telecommunication company serving as the major internet and telephone service provider. Ethio telecom is owned by the Ethiopian government and maintains a monopoly over all telecommunication services in Ethiopia.

Code: AFRO-316634 Type: Ncb - national competitive bidding Language: Amharic Region: Addis ababa city administration Source: Direct posting Security amount: Document amount: Published: 19-Nov-25 (4 hours ago) Deadline: 04-Dec-25 (15 days left)